የትምህርት ቤት መስፈርቶች

Staying up to date on your immunizations is a little thing that can keep everybody healthy. Let's all do the little things.

የትምህርት ቤት እና የህፃናት ማቆያ ዝቅተኛ የክትባት መስፈርቶች

በመንግሥት ወይም በግል የመጀመሪያ፣ መካከለኛ ወይም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ በሕፃናት መቆያ ማዕከላት፣ በመዋለ ሕፃናት፣ በቤተሰብ የቀን እንክብካቤ መስጫዎች ወይም በዕድገት ማዕከላት ለመገኘት ከዚህ በታች ለተጠቀሱት ክትባቶች እንደየዕድሜው የሚወሰደው ትክክለኛ የክትባት መጠን መወሰዱን የሚያረጋግጥ የጽሑፍ ማስረጃ መቅረብ አለበት።  ክትባቶች መሰጠት ያለባቸው ከሚከተሉት ጋር በሚስማማ እንዲሁም የዕድሜ መስፈርት እና በክትባቶች መካከል ሊኖር በሚገባው የጊዜ ልዩነት መሠረት እንዲሁም በእነዚህ መርሐግብር መሠረት ነው፡ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል፣ በAmerica የሕፃናት ሕክምና አካዳሚ (AAP) እና በAmerica የቤተሰብ ሐኪሞች አካዳሚ (AAFP)።

ሕፃናት በአሁኑ AAP ወይም AAFP የክትባት መርሐግብር፣ ወይም በAAP ወይም AAFP የማሟያ መርሐግብሮች መሠረት (ሁሉንም ዝቅተኛ የዕድሜ እና የጊዜ ልዩነት መስፈርቶች ማሟላትን ጨምሮ) የተከተቡ ከሆነ ለትምህርት ቤት መግቢያ ብቁ እንደሆኑ ይቆጠራሉ (ለተጨማሪ መረጃ "ለትምህርት ቤት አስፈላጊ ለሆኑ ክትባቶች ተጨማሪ መመሪያ" የሚለውን ይመልከቱ)።

የእርስዎ ልጅ በየጊዜው በሚያገኘው ክትባት ረገድ ወደኃላ እየቀረ አለመሆኑን ለማረጋገጥ እባክዎን ከጤና እንክብካቤ አቅራቢዎ ጋር ይነጋገሩ።

ክትባትዝቅተኛ መስፈርት
ዲፍቴሪያ፣ ቴታነስ እና ፐርቱሲስ (DTaP፣ DTP፣ ወይም Tdap)ቢያንስ 4 በአግባቡ የተራራቁ የክትባት ዶዞች። አንድ ልጅ በአራተኛው የልደት ቀን ወይም ከዚያ በኋላ ቢያንስ አንድ የDTaP ወይም የDTP ክትባት መውሰድ አለበት። ፐርቱሲስ የያዘ ክትባት (DTaP ወይም DTP) ላለመውሰድ የሕክምና ነፃነት ያላቸው ልጆች የDT(ዲፍቴሪያ፣ ቲታነስ) ክትባት መውሰድ አለባቸው። የቲታነስ እና ዲፍቴሪያ ዝቅተኛ መስፈርቶችን የማያሟሉ 7 ዓመት እና ከዚያ በላይ የሆናቸው ልጆች የአዋቂዎች Tdን መውሰድ ይኖርባቸዋል። ከጁላይ 1 ቀን 2019 ጀምሮ ተፈጻሚ በሆነው መሰረት ወደ 7ኛ ክፍል ለሚገቡ ሁሉም ልጆች የTdap ክትባት ማጠናከሪያ ዶዝ መውሰድ ግዴታ ነው።
ሜኒንጎኮካል ኮንጁጌት (MenACWY)ከጁላይ 1፣ 2021፣ ጀምሮ ቢያንስ 2 ዶዝ የMenACWY ክትባት መውሰድ ያስፈልጋል። የመጀመሪያው ዶዝ ወደ 7ኛ ደረጃ ከመግባት በፊት መሰጠት አለበት። የመጨረሻው ዶዝ ወደ 12ኛ ክፍል ከመግባት በፊት መሰጠት አለበት። ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ተጨማሪ መመሪያ ሰነድ ይመልከቱ።
ሂውማን ፓፒሎማቫይረስ (HPV)ጁላይ 1 ቀን 2021 ጀምሮ ተፈጻሚ በሆነው መሠረት የተሟሉ ተከታታይ 2 የHPV ክትባት ዶዞችን መውሰድ ግዴታ ነው። የመጀመሪያው ዶዝ ልጁ 7ኛ ክፍል ከመግባቱ በፊት የሚሰጥ ይሆናል። አንድ ወላጅ ወይም አሳዳጊ ከጤና ጥበቃ ቦርድ ፈቃድ ያገኙትን ቁሳቁሶች ከተመለከቱ በኋላ በወላጁ ወይም አሳዳጊው ፈቃድ ብቸኛ መሠረት ልጃቸው የHPV ክትባትን እንዳይወስድ መምረጥ ይችላሉ።
ሄፓታይተስ ቢለሁሉም ልጆች የተሟሉ እና ተከታታይ የሆኑ በአግባቡ የተራራቁ 3 የሄፓታይትስ ቢ ክትባት ዶዞችን መውሰድ ይኖባቸዋል። ይሁን እንጂ FDA የ 2-ዶዝ መርሃ ግብርን የፈቀደው ከ 11-15 ዓመት ላሉ ታዳጊዎች ብቻ እና የMerck Brand (RECOMBIVAX HB) የሄፓታይተስ ቢ ክትባት የአዋቂዎች ቅምር ጥቅም ላይ በሚውልበት ጊዜ ብቻ ነው። የ 2-ዶዝ መርሃ ግብሩ ከ 11-15 ዓመት ዕድሜ ላላቸው ታዳጊዎች ጥቅም ላይ ከዋለ ይህ በትምህርት ቤት ቅጹ ላይ በግልጽ መመዝገብ አለበት።
ኩፍኝ፣ ጆሮ ደግፍ እና (MMR)ቢያንስ 2 የኩፍኝ፣ 2 የጆሮ ደግፍ እና 1 የሩቤላ ክትባት። (አብዛኛውን ጊዜ የሚሰጠው ክትባት የተዋሃደ የMMR ክትባት በመሆኑ ምክንያት ብዙዎቹ ልጆች ለእያንዳንዱ ክትባት 2 ዶዝ ይወስዳሉ) የመጀመሪያው ዶዝ በዕድሜ 12 ወራት ወይም ከዚያ በላይ ሲሆኑ መሰጠት አለበት። ሁለተኛው የክትባት ዶዝ መዋዕለ ህፃናት ከመግባት በፊት መሰጠት ያለበት ቢሆንም፣ ነገር ግን በዶዝ 1 እና ዶዝ 2 መካከል መኖር ያለበት ዝቅተኛ የጊዜ ክፍተት ካለፈ በኋላ በማንኛውም ጊዜ መሰጠት ይቻላል።
ሄሞፊለስ ኢንፍሉዌንዛ ታይፕ ቢ (Hib)ይህ ክትባት በዕድሜያቸው እስከ 60 ወራት ድረስ ለሆኑ ህጻናት ብቻ አስፈላጊ ይሆናል። ዋነኛ ተከታታይ ክትባት 2 ወይም 3 ዶዞች ሊኖሩት ይችላሉ (አምራቹን መሰረት በማድረግ)። ሆኖም ግን አስፈላጊ የሚሆኑት ዶዞች የሚወሰኑት ቀደም ብሎ የተሰጡትን ዶዞች ብዛት በመመልከት ሳይሆን ልጁ አሁን ያለበትን ዕድሜ መሰረት በማድረግ ነው። ከ 15 እስከ 60 ወራት መካከል ባለ ዕድሜ ላይ የሚገኙ ያልተከተቡ ህፃናት መውሰድ የሚጠበቅባቸው አንድ የክትባት ዶዝ ብቻ ነው።
ኒውሞኮካል (PCV)ይህ ክትባት አስፈላጊ የሚሆነው በዕድሜያቸው ከ 60 ወራት በታች ለሆኑ ህፃናት ብቻ ነው። የመጀመሪያው ዶዝ የተወሰደበትን ዕድሜ መሰረት በማድረግ ከአንድ እስከ አራት የተቀናጀ የኒውሞኮካል ክትባት ዶዞችን መውሰድ አስፈላጊ ነው።
ሮታቫይረስይህ ክትባት አስፈላጊ የሚሆነው በዕድሜያቸው ከ 8 ወራት በታች ለሆኑ ህፃናት ብቻ ነው። ጁላይ 1 ቀን 2021 ላይ ተፈጻሚ በሆነው መሰረት 2 ወይም 3 የሮቶቫይረስ ክትባት ዶዞችን (አምራቹን መሰረት በማድረግ) መውሰድ ያስፈልጋል።
ፖሊዮ (IPV)ቢያንስ 4 የፖሊዮ ክትባት ዶዞች። አንድ ዶዝ በአራተኛው የልደት ቀን ወይም ከዚያ በኋላ መሰጠት አለበት። ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት የደጋፊ መመሪያ ሰነድን ይመልከቱ።
ቫሪሴላ (ቺከን ፖክስ)ጃኑዋሪ 1 ቀን 1997 ላይ እና ከዚያ በኋላ የተወለዱ ልጆች በሙሉ 12 ወር ሲሞላቸው ወይም ከዚያ በኋላ አንድ የቺክን ፖክስ ክትባት ዶዝ መውሰድ ይኖርባቸዋል። ማርች 3 ቀን 2010 ሁለተኛው ዶዝ መዋዕለ ህፃናት ከመግባት በፊት መሰጠት ያለበት ቢሆንም፣ ነገር ግን በዶዝ 1 እና ዶዝ 2 መካከል መኖር ያለበት ዝቅተኛ የጊዜ ክፍተት ካለፈ በኋላ በማንኛውም ጊዜ መሰጠት ይቻላል።
ሄፓታይተስ ኤ (HAV)ከጁላይ 1 ቀን 2021 ጀምሮ ተፈጻሚ በሆነው መሰረት ቢያንስ 2 የሄፓታይትስ ኤ ክትባት ዶዞች። የመጀመሪያው ዶዝ 12 ወር ዕድሜ ላይ ወይም ከዚያ በኋላ መሰጠት ይኖርበታል።

ለተጨማሪ መረጃ እባክዎን ወደ የክትባት ክፍል በ 1-800-568-1929 (ስቴት ውስጥ ብቻ የሚያገለግል) ወይም 804-864-8055 ይደውሉ።