የእርስዎን የምግብ አገልግሎት ተቋም አመታዊ ፍቃድ በማደስ ላይ

በእርስዎ የVDH የምግብ አገልግሎት ተቋም ማቋቋሚያ ፈቃድ ላይ በተጠቀሰው የማለቂያ ቀን ከመድረሱ በፊት ፈቃድዎን በየዓመቱ ማደስ ያስፈልግዎታል። በየሩብ ዓመቱ መጨረሻ፣ የHampton እና የፔኒሱላ የጤና ዲስትሪክቶች ለፈቃድ ባለቤቶች የክፍያ መጠየቂያ ደረሰኝ በፖስታ ወይም በኢሜይል ይልካሉ፣ ይህም ያሉትን ፈቃዶች እንዲያድሱ ይመክራቸዋል። ያለ ተቀባይነት ያለው ፈቃድ ሥራ እንዳይከናወን፣ ዓመታዊው ፈቃድ ከማለቂያው ቀን በፊት መታደስ አለበት።

የእድሳት ማመልከቻዎን ለማስገባት እነዚህን ደረጃዎች ይከተሉ፡-

ደረጃ 1፦  የ ዓመታዊ የፈቃድ ማመልከቻን ያጠናቅቁ

የምግብ አገልግሎት ፈቃድ ማመልከቻን (Application for Food Service Permit) ማጠናቀቅ እና የ $40 ዓመታዊ የማደሻ ክፍያ መክፈል ይኖርብዎታል።

አዲስ መረጃን እና ለሂሳብ አከፋፈል አላማዎች መከታተል እንዲችሉ የአሁኑን የፖስታ አድራሻ ማካተትዎን እርግጠኛ ይሁኑ።

ደረጃ 2፦ የተጠናቀቀውን የዓመታዊ ፈቃድ ማመልከቻያስገቡ

  • ወደ ኮምፒውተርዎ ይቃኙት (ስካን ያድርጉት) እና ተቋሙ በሚገኝበት ወይም በተመሰረተበት የአካባቢዎ የጤና መምሪያ በኢሜይል ይላኩ። ከዚያም የ$40 ዓመታዊ የፈቃድ ክፍያ በክሬዲት ካርድ ለመክፈል ሥራዎ በተመሰረተበት አካባቢ በመደወል ማከናወን ይችላሉ፤ ወይም
  • እንዲሁም ፈቃዱን ከቼክ ጋር ወደ እርስዎ አካባቢ ቢሮ በፖስታ መላክ ይችላሉ; ወይም
  • ማመልከቻውን ያቅርቡ እና ክፍያውን በቀጥታ በአካባቢው ቢሮ ይክፈሉ.