ኢንፍሉዌንዛ (ጉንፋን) በቨርጂኒያ

ኢንፍሉዌንዛ በተለምዶ ፍሉ ወይም ወቅታዊ ፍሉ ይባላል። በቫይረሶች የሚመጣ ተላላፊ የመተንፈሻ አካላት በሽታ ሲሆን ይህም አፍንጫን፣ ጉሮሮንና ሳንባን ያጠቃል። ጉንፋን ከቀላል እስከ ከባድ ሕመም ሊያስከትል ይችላል፣ እና አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ለሞት ሊዳርግ ይችላል። ጉንፋን በዋናነት የሚተላለፈው ጉንፋን ያለባቸው ሰዎች ሲስሉ፣ ሲያስነጥሱ ወይም ሲያወሩ በሚፈጠሩ ጠብታዎች ነው።

ማንኛውም ሰው ጉንፋን ሊይዘው ይችላል፣ ነገር ግን በትናንሽ ልጆች፣ በአረጋውያን፣ ሥር የሰደዱ በሽታዎች (ለምሳሌ የሳንባ በሽታ፣ የልብ ሕመም፣ ካንሰር ወይም የስኳር በሽታ) እና የበሽታ መከላከያ ስርዓታቸው በተዳከመባቸው ሰዎች ላይ በጣም ከባድ ነው።

የኢንፍሉዌንዛ በሽታን ለመከላከል በጣም ጥሩው መንገድ በየዓመቱ የኢንፍሉዌንዛ ክትባት መውሰድ ነው።  ጥያቄዎች ካሉዎት የጤና እንክብካቤ አቅራቢዎን ያነጋግሩ።